የሳልመኔ ከተማ ማዘጋጃ ጽ/ቤት - አጠቃላይ መረጃ

የሳልመኔ ከተማ አጠቃላይ መረጃ

አጠቃላይ የከተማ ሁኔታ፣ የልማት አቅጣጫዎች እና የአገልግሎት መዋቅሮች

መግቢያ

ሳልመኔ ከተማ በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን አስተዳደር ከሚገኙ ወረዳዎች ውስጥ በአብልኮ ወረዳ አስተዳደር ስር የምትገኝ ስትሆን በ2001 ዓ.ም መዘጋጃ ቤት ተቋቁሞላት ወደ ስራ በመግባት ቀጥሎም የአብልኮ ወረዳ መቀመጫ በመሆን ለነዋሪወቿ የማህበራዊ የተለያዩ የአስተዳደር ማዕከል ሁና እያገለገለች ትገኛለች፡፡

የከተማዋ የእድገት ፕላን ከአሁን በፊት በ2001 ዓ.ም ተዘጋጅቶ ቢሆንም የፕላን ዘመኑ በመጠናቀቁ ምክኒያት እና የተዘጋጁ ፕላኖችንም ቢሆኑ ወቅቱን ጠብቆ ክለሳ ማድረግ ካልተቻለ በየጊዜው እየጨመረ ከሚሄደው የህዝብ ቁጥር እድገትና ፍላጎት ጋር ተመጣጣኝ የሆነ አገልግሎት መስጠት ስለማይቻል የክለሳ ፕላን መስራት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

ዋና ዋና ቁጥራዊ መረጃዎች

98,640 ህዝብ (2014 ዓ.ም)
49,182 ሄ/ር ስፋት
18 ቀበሌዎች
2,200-3,000 ሜትር ከፍታ

መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ

የሳልመኔ ከተማ በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን አስተዳደር ከሚገኙ ወረዳዎች ውስጥ በአብልኮ ወረዳ አስተዳደር ስር የምትገኝ ስትሆን፡-

  • አንፃራዊ መገኛ፡ በደቡብ ሰሜን ሸዋ ዞን፣ በሰሜን ደሴ ዙሪያና የቃሉ ወረዳ፣ በምስራቅ ኦሮሚያ ዞን እና በምዕራብ ወረኢሉ ወረዳዎች ጋር ይዋሰናል።
  • ከባህር ወለል በላይ ከፍታ፡ 2,200 ሜትር እና 3,000 ሜትር መካከል
  • የመልክዓ ምድር ገፅታ፡ 27% ሜዳማ፣ 27% ተራራማ፣ 46% ሸለቋማ
  • የአየር ንብረት፡ 76.8% ወይና ደጋ፣ 11.44% ደጋ፣ 11% ቆላ፣ 0.76% ውርጭ
  • ዓመታዊ የዝናብ መጠን፡ 900-1400 ሚሜ

የውሃ ሀብት እና የተፋሰስ ሁኔታ

በአልቡኮ ወረዳ ውስጥ 10 ወንዞች የሚገኙ ሲሆን እነዚህም፡-

የወንዙ ስም ተፋሰስ ሊያለሙ የሚችሉት መሬት (ሄ/ር)
ገላና አዋሽ 65.5
አባሰደን ተፋሰስ አዋሽ 23.59
ሸጠልማጥ አባይ 47.25
ሴሱ አዋሽ 65.5
በብልኮ አዋሽ 25.6

በወረዳው አንድ ማይባር የተሰኘ ሀይቅ ይገኛል፡፡ አጠቃላይ 418.25 ሄ/ር መሬት ማልማት ተችሏል፡፡

የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ

የግብርና ሁኔታ
  • የታረሰ መሬት፡ 17,853 ሄ/ር (31.3%)
  • ዋና ዋና ሰብሎች፡ ጤፍ፣ ስንዴ፣ ገብስ፣ በቆሎ፣ ጥራጥሬ
  • የምርት አቅም፡ 424,292 ኩ/ል (2013/14 ዓ.ም)
  • የነፍስ ወከፍ ምርት፡ 4.3 ኩ/ል
የእንሰሳት ሀብት
  • አጠቃላይ ብዛት፡ 261,924
  • የዳልጋ ከብት፡ 53,992 (20.6%)
  • በግ፡ 83,032 (31.7%)
  • ደሮ፡ 78,524 (29.97%)
  • ፍየል፡ 29,555 (11.28%)
የንግድ እና ኢንዱስትሪ ሁኔታ
  • ፍቃድ ያሳደሱ ነጋዴዎች፡ 681
  • ፍቃድ ያላሳደሱ ነጋዴዎች፡ 868
  • የተፈጠረ የስራ ዕድል፡ 1,549
  • ዋና የንግድ መስኮች፡ ችርቻሮ፣ አገልግሎት፣ ኢንዱስትሪ፣ ግብርና ልማት

የማዘጋጃ ቤት ድርጅታዊ መዋቅር

ዋና ዋና ክፍሎች
የመሬት አገልግሎት ክፍል

የመሬት መወሰን፣ መለያ ማድረግ እና ቁጥጥር አገልግሎቶች

የግንባታ ፈቃድ ክፍል

የግንባታ ፈቃድ መስጠት እና ቁጥጥር አገልግሎቶች

የንግድ ፈቃድ ክፍል

የንግድ ፈቃድ መስጠት እና እድሳት አገልግሎቶች

ሌሎች ክፍሎች
የመሠረተ ልማት ክፍል

መንገድ፣ ውሃ፣ መብራት እና ፖስታ አገልግሎቶች

ማህበራዊ አገልግሎት ክፍል

ትምህርት፣ ጤና እና ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች

የገቢ ጽ/ቤት

የገቢ ማሰባሰብ እና አስተዳደር

የልማት የጊዜ መስመር

2001 ዓ.ም
የማዘጋጃ ቤት መቋቋም

ሳልመኔ ከተማ መዘጋጃ ቤት ተቋቁሞላት ወደ ስራ በመግባት የአብልኮ ወረዳ መቀመጫ ሆነች፡፡

2001 ዓ.ም
የመጀመሪያ የእድገት ፕላን ዝግጅት

የከተማዋ የመጀመሪያ የእድገት ፕላን ተዘጋጅቶ ተግባራዊ ውሏል፡፡

2014 ዓ.ም
የክለሳ ፕላን ጥናት መጀመር

የከተማዋን ሁኔታ የሚያጤን የክለሳ ፕላን ጥናት ተጀምሯል፡፡

2016 ዓ.ም
የክለሳ ፕላን ማስተዋወቂያ

የሳልመኔ ከተማ ክለሳ ፕላን (2014-2024 ዓ.ም) ለህዝብ ይቀርባል፡፡

2024 ዓ.ም
የክለሳ ፕላን የማጠናቀቂያ ዓመት

የክለሳ ፕላን ዘመን ያበቃል እና አዲስ ፕላን ይጠናቀቃል፡፡